A sample Guide How To Write a Report.pptx

solzem 12 views 16 slides Aug 31, 2025
Slide 1
Slide 1 of 16
Slide 1
1
Slide 2
2
Slide 3
3
Slide 4
4
Slide 5
5
Slide 6
6
Slide 7
7
Slide 8
8
Slide 9
9
Slide 10
10
Slide 11
11
Slide 12
12
Slide 13
13
Slide 14
14
Slide 15
15
Slide 16
16

About This Presentation

a Sample Guide How to Write a Report.pptx


Slide Content

የ2017 ዓ.ም ደ/ጎ/ ዞን የአስተዳደር ቁጥር 1 የብልፅግና ህብረት ዓመታዊ ሪፖርት በሃምሌ 2017 ዓ.ም

የብልፅግና ህብረት የአስተዳደር ቁጥር 1 ሪፖርት የድርጅቱን እንቅስቃሴዎች ፣ አላማዎች ፣ ጥንካሬዎች እና ድክመቶች ይዳስሳል። በሃምሌ 2017 ዓ.ም

መግቢያ ድርጅታችን በአባላቱ መካከል ህብረትና ትብብርን በማጠናከር ሃገራዊና አለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው በማድረግ ፓርቲያችን እንዲጠናከር እና አባላት የመንግስትና የፓርቲ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን በመረዳትና በመተግበር ግንባር ቀደም ሚና መወጣት ይኖርባቸዋል ፡፤ በዚህም መሰረት የአስተዳደር ቁጥር 1 ህብረት ውስጥ የተደራጀን አባላት አመለካከትና የአስተሳሰብ ቁመናቸው በማሻሻል የተለያዩ ተልዕኮዎችን እንዲፈፅሙ እየተደረገ ይገኛል ። ስለሆነም የህብረቱ አመራር እና አባላት በ2017 በጀት ዓመት የነበሩነን ጥንካሬዎች በማሰቀጠል ድክመቶቻችን በማረም እና በማስተካከል 2018 ዓ.ም የፓርቲ ስረዎቻችን የተሻለ / የመሪነት / ሚና እንዲኖራቸው አፈፃፀ ሞ ችን በአግባቡ መገምገም እና አቅጣጫ ማስቀመጥ በማስፈለጉ ይህ የግምገማ ሰነድ ተዘጋጅታዋል ፡፡

ዓላማ 1 ጠንካራ ህብረት መፍጠር የቤተሰብ አባላትን አቅም ማሳደግ፣ የፓርቲ ዲሲፕሊንን መጠበቅ፣ ሙያዊ ስነ-ምግባርን ማዳበር፣ በሁሉም መስኮች ተባብሮ መታገል፣ ጠንካራና ግንባር ቀደም እንዲሆኑ በማድረግ የሚሠጣቸውን የፓርቲ ተልዕኮና ተግባር በውጤታማት መፈፀማቸውን ማረጋገጥ ። 2 የፖለቲካ ጤንነትን ማዳበር የቤተሰብን አሰራር በማጠናከር የአባላትን የፖለቲካ ጤንነትና አቅም መገንባት፣ ብልሹ አሰራርንና ሌብነትን መታገል፣ የአባላትን ርዕዮተ ዓለማዊና ፖለቲካዊ ብቃት ማሳደግ።

የህብረቱ አባላት ብዛት ኮሙዩኒኬሽን ወ፡-3 ሴ፡-8 ድ፡- 11 ብልፅግና ወ፡-3 ሴ፡-7 ድ፡-10 ሚሊሻ ወ፡-14 ሴ፡- 4 ድ፡- 18 ሰላምና ደህንነት ወ፡- 14 ሴ፡- 8 ድ፡- 22 አስተዳደር ወ፡-24 ሴ፡- 22 ድ፡-46 በአስተዳደር ቁጥር 1 ውስጥ የሚገኙ የህብረቱ አባላት ብዛት በተለያዩ ዘርፎች እንደሚታየው ነው። አስተዳደር በ46 አባላት ከፍተኛውን ቁጥር ይይዛል።

የተከናወኑ ተግባራት የ2017 ዓ.ም ከፓርቲው የተላከውን እቅድ መነሻ በማድረግ እንደ ህብረት የህብረቱ ዓመራሮች በጋራ በመሆን እቅድ አቅዶ ወደ ስራ መግባት የህብረቱን ልዩ ልዩ መረጃዎች አደራጅቶ ወደ ስራ መግባትን የቤተሰብ አባላት ከሚልኩት ሪፖርት በመነሳት በየወሩ ግብረ መልስ መስጠት እና በአካልም ድጋፍና ከትትል ማድረግ ከቤተሰብ አባላት ጋር ያለውን የስራ ግንኙነት የተሻለ መሆኑ

የቀጠለ ……. የቤተሰብ አባላት በወር 2 ጊዜ ፓርቲው በሚያወርዳቸው የመወያያ ርእሶች ያልተቋረጠ ውይይት በመወያየት አባላት የፖለቲካ አቅማቸውን እንዲገነቡ ማድረግ በየሩብ ዓመቱ የሂስ ግለሂስ እና የደረጃ ምደባ እንዲካሄድ መደረጉ የቤተሰብ አባላት የፅንፈኝነት አስተሳሰብ እንዳይኖራቸውና በሚካሄዱት የህብረቱ ውይይቶች ላይ ሀሳባቸውን በነፃነት እንዲያራምዱ የማድረግ ስራ መሰራቱ የፖለቲካ አቅማቸውን እንዲገነቡና የፓርቲውን አላማና ግብ በውል እንዲረዱ በየጊዜው ውይይቶች መካሄዳቸው

የቀጠለ ……. ከቤተሰብ አባላት ውስጥ በተግባር ግንባር ቀደሞችን በአሰራርና አደረጃጃት መምሪያ መሰረት መመልመል እና እስቶክ ለሚመለከተው አካል መላክ በህብረቱ አባላት ለማፍራት የተደረገው ጥረት አበረታች መሆኑ ፡- ለአብነት አስተዳደር ጽ/ቤት፣ኮሙዩኒኬሽን፣ አባላት መፈራቱ ሁሉም የቤተሰብ አባላት መፅሄቶችን እንዲያነቡ ውስጣዊ መነሳሳት በመፍጠር የፖለቲካ ርእዮት አለም ብቃታቸው እንዲያሳድጉ መደረጉ ሁሉም የቤተሰብ አባላት ወርሃዊ ክፍያቸውን ማንንም ሳይጠብቁ መክፈል መቻላቸው የቤተሰብ አባላት መረጃ ፓርቲው ባዘጋጃቸው አዳዲስ ፎርማቶች በሀርድ ኮፒ ና በሶፍት ኮፒ ተለይተው በፎቶ ግራፍ የተደገፈ መረጃ መያዙ

የነበሩ ጥንካሬዎች በ2017 ዓ.ም የህብረቱ አመራሮች በተደራጀ መንገድ ተግባራትን መስራት መቻላቸው እና በሰነድነት መያዛቸው የቤተሰብ አባላት ልዩ ልዩ መረጃዎች በአግባቡ መደራጀታቸው የቤተሰብ አባላት ውይይታቸውን ሳያቆራርጡ እንዲካሄድ ደጋፊ ቡድን በማዘጋጀት መከታተል መቻሉ የቤተሰብ አባላት በየወሩ ከሪፖርታቸው በመነሳት ግብረ-መልስ መሰጠቱ የቤተሰብ የሚያደርጉት ውይይት ሰፊና ለፓርቲው ግብዓት የሚሆኑ ውይይት መካሄዱ

የቀጠለ …… ከፓርቲ ጽ/ቤት ጋር የሪፖርት ፣የግብረ-መልስ የቸክ-ሊስት እንዲሁም የአካል ድጋፍ በጥሩ ሁኔታ መሰራታቸው እንደ ህብረት ሰፋፊ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸው የቤተሰብ አባላት በወቅቱ ፋይናንስ በመክፈል እና ፓርቲው የሚዘጋጃቸውን ልሳናት በመግዛት የተሻለ ቁመና ነበራቸው

የታዩ ድክመቶች የቤተሰብ አባላት ሪፖርት በወቅቱ አለማድረስ ፡- ለምሳሌ ፡- ጉና ጥብቅናሰላምና ደህንነት፣ሚሊሻ የቤተሰብ አባላት የሪፖርት ፎርማቱን ጠብቆ ሪፖርት አለማዘጋጀት የቤተሰብ አባላት በተሰጣቸውን የአካልና የስልክ ድጋፍ ወስዶ አለመስራትና በፍጥነት ወደ ስራ አለመግባት ችግሮች መኖራቸው በልሳናት ተነባቢነትና እራሳን በማብቃት የትኩረት ችግር መኖሩ የቤተሰብ አባላት 100 ፐርሰንት አባላትን ማፍራት አለመቻሉ

ተሞክሮዎች ወጥ የሆነ የሪፖርት ስርዓት መዘርጋት መቻሉ ሰላምና ፀጥታ ፣ ሚሊ ሻ ና ብል ጽ ግና ስራተኛቸውን ሁሉም የቤተሰብ አባላት ማድረግ መቻላቸው ፤ በሀብረቱ ኮንፍረንሶች አባሉ በመከታተልና በመገኘት እንዲሁም በንቃት በመሳተፍ የተሻለ መሆኑ ፤ በ ህብርት ደረጃ ችክሊስት አየተዘጋጀ ቤተሰቦች መደገፋቸው ፤ ቤተሰቦችን የሚደግፉ የሀብረቱ አመራሮቸ ተመድበው መደገፍ መቻላቸው ፤

የቀጣይ አቅጣጫዎች 1 ወርሃዊ ክፍያ ወርሃዊ የአባልነት ክፍያዎችን በወቅቱ መክፈል ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። 2 የአባላት መጨመር የአባላት ቁጥር እንዲጨምር የግንዛቤ ስራ መስራትና አባላትን አዲስ ማፍራት ያስፈልጋል። 3 የአባልነት ግዴታ የአባልነት ግዴታን መወጣት ፤ የፓርቲ ተልዕኮዎችን በአግባቡ ተቀብሎ በቁርጠኛነት መፈፀም ይጠበቃል። 4 የቤተሰብ ውይይት በወር 1 ጊዜ በሚደረገው የቤተሰብ ውይይት ላይ በንቃት ተሳታፊ መሆን ያስፈልጋል። የፓርቲው መድረኮች ላይ አባላት ሐሣባቸውን በነፃነት እንዲያራምዱ ማድረግ፤ አዲስ የሪፖርት ፎርማት ማዘጋጀት እና ሁሉም የቤተሰብ አባላት ሪፖርት በወቅቱ እንዲያደርሱ ማድረግ ይገባል።

የቀጠለ ……… የሥራ እቅዶችን ለማሳካት በሚደረገው እንቅስቀሴ ውስጥ ግንባር ቀደም ሆኖ መንቀሳቀስ ፤ የሥራ ቸክ-ሊስት በየወሩ አያዘጋጁ ለፈፃሚዎች መስጠት፤/በቸከ-ሊስትብዛት/ ከፓርቲው የሚወርዱ የተለያዩ ተልዕኮዎችን ተቀብሎ በቁርጠኛነት መፈፀም ፤ የቤተሰብ አባላት የአፈፃፀም ግምገማ ፤ የግለ-ሒስና የሒስ መድረክን በማመቻቸት አባላትን በተግባር እያበቁና ለተልዕኮ እያዘጋጁ መሄድ ፤ ለህብረቱና ለዞን ፓርቲ ቅር/ጽ/ቤት መድረስ ያለባቸውን መረጃዎች ፤ ሪፖርቶችና ደብዳቤዎች ከእውነተኛ መረጃ በመነሣት አዘጋጅተን መላክ ፤ የአስተዳደር ቁጥር 1 የብልፅግና ህብረት የቤተሰብ አባላትን እንቅስቃሴ በማጠናከር ውጤታማ ተግባራት እንዲሠሩ ማድረግና ከቤተሰብ አባላት የሚጠበቀውን ሰርቶ መገኘት ፤

ማጠቃለያ በ2017 ዓ.ም የብልፅግና ህብረት በብዙ ዘርፎች አስፈላጊ ስራዎችን ቢያከናውንም፣ በሪፖርት ማቅረብ፣ በግንኙነት እና በአባላት ቁጥር ማሳደግ ላይ ተጨማሪ ማሻሻል ያስፈልጋል። የወደፊቱ እቅዶች በተግባር ላይ ከተከናወኑ፣ ድርጅቱ የበለጠ ውጤታማነት እንደሚያሳድግ ይጠበቃል። በአጠቃላይ በ2017 ዓ.ም እንደዞን የጸጥታ ችግር ቢኖርም በአሰ/የብልፅግና ህብረት የተከናወኑ ተግባራት አርዕያነት ያላቸዉ ናቸዉ፡፡ የፓርቲ ና የመንግስት ተግባሮች አቀናጅቶ በመምራት   በኩልም እደህብረቱ ወስደን ስናዬው የተሻለነው ብሎ መውሰድ ይቻላል ። ይሁን እንጅ ፓርቲያችን የመሪነት ሚኒናውን ይዞ እንዲቀጥልና የመንግስት ተግባራትን ከፊት ሆኖ ለመምራት የህብረት አደረጃጀትና የቤተሰብ አደረጃጀት ተጠናክረው በስራችው ያለውን አባላት በርጠኝነትና በታማኝነት በአላማ ጽናት ተግባራትን እንዲያከናውን የለት ከለት ክትትልና ድጋፍ ግምገማ ማድረግ ግድ ይላላ ። በመሆኑም በ2018 በጀት አመት የፓሪቲያችን ተልኮ በውጤታማነት ለመፈጸም የሁላችንም የፓርቲ አባላት ተሳትፎና ፈፃሚነትን በቁርጠኝነት መያዝ ያስፈልጋል ።

እናመሰግናለን! ስለተሳተፉ እናመሰግናለን።