New Microsoft PowerPoint Presentation.pptx

AbdissaGaromsa 0 views 11 slides Oct 04, 2025
Slide 1
Slide 1 of 11
Slide 1
1
Slide 2
2
Slide 3
3
Slide 4
4
Slide 5
5
Slide 6
6
Slide 7
7
Slide 8
8
Slide 9
9
Slide 10
10
Slide 11
11

About This Presentation

ማንቸስትር ሲቲ ከ ክርስቲያል ፓላስ ባደረጉት ጨዋታ 5ለ2 ሰፊ በሆነ ጎሎች ተጠናቋል ጎሎቹን ዴ ብሮይነ ኦማር ማርሙሽ ኮቫቺች ማክቲ እና ኦራይሊ የማንቸስትር ስቲን ጎሎች ያስቆጠሩ ሲሆን 2�...


Slide Content

ትላንት በተደረገው የ ኢሮፓ ሊግ ጨዋታ ማንቸስትር ዩናይትድ ከ ኦሎምፒክ ሊዮን 2አቻ የተጠናቀቀ ሲሆን መጀመሪያ ለሊዮን ቲያጎ አልማዳ ሲያስቆጥር ከዛ ሌኒ ዮሮ እና ጆሽዋ ዚርክዚ ሲያስቆጥሩ በመጨረሻ ራያን ቼርኪ አቻ አድርጓል። የማንቸስተር ዩናይትድ እና የኦሎምፒክ ሊዮን ጨዋታ

የሌጋኔስ እና የባርሴሎና ጨዋታ ባርሴሎና መሪነቱን አጠናክሯል ! የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ከሌጋኔስ ጋር ያደረጉትን የላሊጋ መርሐግብር 1ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል። የባርሴሎናን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ሴንዝ በራሱ ግብ ላይ ከመረብ አሳርፏል። ባርሴሎና ማሸነፉን ተከትሎ ከሪያል ማድሪድ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሰባት ማስፋት ችሏል። በጨዋታው የባርሴሎናው ተጨዋች አሌሀንድሮ ባልዴ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ ለመውጣት ተገዷል። የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ? 1️⃣ ባርሴሎና :- 70 ነጥብ 1️⃣9️⃣ ሌጋኔስ :- 28 ነጥብ ቀጣይ መርሐግብር ? ቅዳሜ - ባርሴሎና ከ ሴልታቪጎ ቅዳሜ - ማዮርካ ከ ሌጋኔስ @ Tikvahethsport     @ kidusyoftahe

ማንቸስተር ሲቲ ወሳኝ ድል አሳክቷል ማንቸስትር ሲቲ ከ ክርስቲያል ፓላስ ባደረጉት ጨዋታ 5ለ2 ሰፊ በሆነ ጎሎች ተጠናቋል ጎሎቹን ዴ ብሮይነ ኦማር ማርሙሽ ኮቫቺች ማክቲ እና ኦራይሊ የማንቸስትር ስቲን ጎሎች ያስቆጠሩ ሲሆን 2ቱን ከሽንፈት ያልታድጉ ኤቤሬ ኤዜ እና ሪቻርድስ ለፓላስ አስቆጥረዋል

የሬንጀርስ እና የአትሌቲክ ቢልባኦ ጨዋታ ሬንጀርስ ከ አትሌቲክ ቢልባዎ 0 አቻ የትጠናቀቀ ሲሆን በ ሬንጀርስ በኩል ሮቢን ፕሮፐር ቀይ ካርድ ተመልክቷል ቶተንሃም ሆትስፐር ከ ኢንትራክት ፍራንክፉርት 1 አቻ የተጠናቀቀ ሲሆን የቶተንሃምን ጎል ፔድሮ ፖሮ ሲያስቆጥር የኢንትራክት ፍራንክፉርትን ጎል ደግሞ ሁጎ ኢኪቴኬ አስቆጥሯል

የቦዶ ግሊምት እና የላዚዮ ጨዋታ ቦዶ ግሊምት ከ ላዚዮ ባደረጉት ለላው የ ኢሮፓ ሊግ ጨዋታ ቦዶ ግሊምት 2ለ0 ስታሸንፍ ኡልሪክ ሳልትነስ 2ቱን ጎሎች አስቆጥሯል

የኮንፍረንስ ሊግ ጨዋታዎች መጀመሪያ ቼልሲ ሌጊአ ዋርሳውን 3ለ0 ስታሸንፍ የቼልሲን ጎሎች ቲርኪዩ ጆርጅ እና ኖኒ ማዱዌኬ 2ጎሎችን አስቆጥረዋል ኤንኬ ሴልጄ ከ ፊዮረንቲና 2ለ1 ፊዮረንቲና አሸንፏል ሪያል ቤቲስ ጃጊዬሎኒያን 2ለ0 አሸንፏል ድጁርገን በ ራፒድ ቬኢን 1ለ0 ተሸንፏል

ባየር ሌቨርኩሰን ነጥብ ጥለዋል ባየር ሌቨርኩሰን ከዩኒየን በርሊን ጋር ያደረገውን ጨዋታ 0ለ0 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል። ባየር ሌቨርኩሰን ከሊጉ መሪ ባየር ሙኒክ ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሶስት ማጥበብ የሚችልበትን እድል ሳይጠቀም ቀርቷል። ባየር ሌቨርኩሰን በስልሳ ሶስት ነጥቦች ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። የሌሎች የቡንደስሊጋ ጨዋታዎች ውጤት ከታች ተያይዟል ። ቦኩም 1 ኦግስበርግ 2 ሞንችካላብራክ 1 ፍራይይበርግ 2 Tsg ሆፈናየም 2 ሜንዝ 0 ሆስትን ኪል 1 ሰንት ፓውሊ 2

የእንግሊዝ ፕሬመርም ሊግ ጨዋታዎች Full time በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐግብር አስቶንቪላ ከሳውዝሀምፕተን ጋር ያደረገውን ጨዋታ 3ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፏል። የአስቶን ቪላን የማሸነፊያ ግቦች ኦሊ ዋትኪንስ ፣ ማለን እና ማክጊን አስቆጥረዋል። በሌላ ጨዋታ ኤቨርተን በዱኩሬ ግብ ኖቲንግሀም ፎረስትን 1ለ0 አሸንፏል። ኖቲንግሀም ፎረስት ሁለተኛ ተከታታይ ሽንፈቱን አስተናግዷል። ብራይተን በበኩሉ ከሌስተር ሲቲ ጋር 2ለ2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል። @ Tikvahethsport      @ kidusyoftahe#Premiereleague በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐግብር አስቶንቪላ ከሳውዝሀምፕተን ጋር ያደረገውን ጨዋታ 3ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፏል። የአስቶን ቪላን የማሸነፊያ ግቦች ኦሊ ዋትኪንስ ፣ ማለን እና ማክጊን አስቆጥረዋል። በሌላ ጨዋታ ኤቨርተን በዱኩሬ ግብ ኖቲንግሀም ፎረስትን 1ለ0 አሸንፏል። ኖቲንግሀም ፎረስት ሁለተኛ ተከታታይ ሽንፈቱን አስተናግዷል። ብራይተን በበኩሉ ከሌስተር ሲቲ ጋር 2ለ2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል። @ Tikvahethsport      @ kidusyoftahe

የኤዲ ሃው ህመም አሰልጣኝ ኤዲ ሀው ህመም አጋጠማቸው ! የኒውካስል ዩናይትዱ ዋና አሰልጣኝ ኤዲ ሀው የነገውን የማንችስተር ዩናይትድ ጨዋታ እንደማይመሩ ይፋ ተደርጓል። አሰልጣኝ ኤዲ ሀው በጨዋታው የማይገኙት ባጋጠማቸው ህመም ምክንያት መሆኑ ተገልጿል። አሰልጣኝ ኤዲ ሀው ትላንት ሌሊት ህመም አጋጥሟቸው ወደ ሆስፒታል ማምራታቸው ተገልጿል። አሰልጣኙ አሁን ላይ ሆስፒታል የህክምና ምርመራ እየተደረገላቸው መሆኑን ክለቡ አረጋግጧል።

የአርሰናል እና ብሬንትፎርድ ጨዋታ መድፈኞቹ ነጥብ ጥለዋል ! የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ከብሬንትፎርድ ጋር የፕርሚየር ሊግ መርሐግብር 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቋል። የመድፈኞቹን ግብ ቶማስ ፓርቴ ሲያስቆጥር ዊሳ ብሬንትፎርድን አቻ አድርጓል። አርሰናል በውድድር ዘመኑ አስራ ሁለተኛ የፕርሚየር ሊግ ጨዋታቸውን በአቻ ውጤት አጠናቀዋል። የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ? 2️⃣ አርሰናል :- 63 ነጥብ 1️⃣1️⃣ ብሬንትፎርድ :- 43 ነጥብ ቀጣይ መርሐግብር ? እሁድ - ኢፕስዊች ከ አርሰናል ቅዳሜ - ብሬንትፎርድ ከ ብራይተን @ tikvahethsport      @ kidusyoftahe

የዶርትሙንድ እና የባየር ሙኒክ ጨዋታ ባየር ሙኒክ ከዶርትመንድ አቻ ተለያይተዋል ! በጀርመን ቡንደስሊጋ ሀያ ዘጠነኛ ሳምንት መርሐግብር ባየር ሙኒክ ከቦርስያ ዶርትመንድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2ለ2 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል። የባየር ሙኒክን ግቦች ግናብሪ እና ጉሬሮ ሲያስቆጥሩ ለቦርስያ ዶርትመንድ ቤር እና አንተን ከመረብ አሳርፈዋል። የሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ ምን ይመስላል ? 1️⃣ ባየር ሙኒክ :- 69 ነጥብ 8️⃣ ዶርትመንድ :- 42 ነጥብ ቀጣይ መርሐግብር ? ቅዳሜ - ሄደንሄም ከ ባየር ሙኒክ እሁድ - ዶርትመንድ ከ ሞንቼ ግላድባህ @ Tikvahethsport     @ kidusyoftahe
Tags